MAHIBERE_KIDUSAN Telegram 8502
26 የደረጃ አንድ የሰባኪያነ ወንጌል ሠልጣኞች መመረቃቸውን በማኅበረ ቅዱሳን የአርባምንጭ ማእከል ገለጸ

የካቲት ፲፫/፳፻፲፯ ዓ.ም

በማኅበረ ቅዱሳን የአርባምንጭ ማእከል ከከምባ ወረዳ ማእከል ጋር በመተባበር በከምባና ጋርዳ ማርታ ወረዳዎች፣ ከተለያዩ አጥቢያዎችና የስብከት ወንጌል መስጫ ማእከላት ለተወጣጡ 26 የደረጃ አንድ የሰባኪያነ ወንጌል ሠልጣኞች የካቲት 12 ቀን /2017 ዓ.ም አስመርቋል ::

በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ የማኅበረ ቅዱሳን አርባምንጭ ማእከል ተወካይ፣ የከምባ ወረዳ ቤተክህነት ተወካይ እና የከምባ ወረዳ ማእከል ስራ አስፈጻሚዎች ተገኝተዋል።

በመርሐ ግብሩ በሠልጣኞች አጠር ያለ ትምህርተ ወንጌል የተሰጠ ሲሆን  ከአርባምንጭ ማእከል ስብከተ ወንጌል ዋና ክፍል በመ/ር መብራቱ “እኔ ከምሰጠው ውሃ የሚጠጣ ሁሉ ለዘለዓለም አይጠማም” በሚል ርዕስ ት/ተ ወንጌል ተሰጥጧል።

የከምባ ወረዳ ማዕከል ሰብሳቢ አቶ ቸርነት ጫሬ የወረዳ ማእከሉን መልዕክት አስተላልፈው ሥልጠናው የአርባምንጭ ማእከል ከከምባ ወረዳ ማእከል ጋር በጋራ እንደተዘጋጀ  በመግለጽ አርባምንጭ ማእከልን አመስግነዋል።

የማኅበረ ቅዱሳን አርባምንጭ ማእከል ጽ/ቤት ኃላፊ  ዲ/ን ችሮት አበራ በመልእክታቸው ማ/ቅ አርባምንጭ ማእከል በእግዚአብሔር ቸርነት ላለፉት 5 ወራት ከሚመለከታቸው የቤ/ን አካላት ጋር በመተባበር 8364 አዳዲሰ አማንያን ወደ ቅድስት ቤ/ክን እንዲቀላቀሉ አድርጓል በማለት በተጨማሪም ሌሎችም በርካታ መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎቶች መከናወናቸውን ጠቁመዋል።

አክለውም  በእንደዚህ አይነት ሐዋርያዊ አገልግሎት በዛሬው ዕለት የተመረቁ ሰባኪያነ ወንጌል በሚሰማሩበት አከባቢ በቋንቋቸው  በማስተማር  ለቅድስት ቤ/ክ ትልቅ ሚና እንዳላቸው ገልጸው ጠንክረው እንዲያገለግሉ መክረዋል።



tgoop.com/mahibere_kidusan/8502
Create:
Last Update:

26 የደረጃ አንድ የሰባኪያነ ወንጌል ሠልጣኞች መመረቃቸውን በማኅበረ ቅዱሳን የአርባምንጭ ማእከል ገለጸ

የካቲት ፲፫/፳፻፲፯ ዓ.ም

በማኅበረ ቅዱሳን የአርባምንጭ ማእከል ከከምባ ወረዳ ማእከል ጋር በመተባበር በከምባና ጋርዳ ማርታ ወረዳዎች፣ ከተለያዩ አጥቢያዎችና የስብከት ወንጌል መስጫ ማእከላት ለተወጣጡ 26 የደረጃ አንድ የሰባኪያነ ወንጌል ሠልጣኞች የካቲት 12 ቀን /2017 ዓ.ም አስመርቋል ::

በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ የማኅበረ ቅዱሳን አርባምንጭ ማእከል ተወካይ፣ የከምባ ወረዳ ቤተክህነት ተወካይ እና የከምባ ወረዳ ማእከል ስራ አስፈጻሚዎች ተገኝተዋል።

በመርሐ ግብሩ በሠልጣኞች አጠር ያለ ትምህርተ ወንጌል የተሰጠ ሲሆን  ከአርባምንጭ ማእከል ስብከተ ወንጌል ዋና ክፍል በመ/ር መብራቱ “እኔ ከምሰጠው ውሃ የሚጠጣ ሁሉ ለዘለዓለም አይጠማም” በሚል ርዕስ ት/ተ ወንጌል ተሰጥጧል።

የከምባ ወረዳ ማዕከል ሰብሳቢ አቶ ቸርነት ጫሬ የወረዳ ማእከሉን መልዕክት አስተላልፈው ሥልጠናው የአርባምንጭ ማእከል ከከምባ ወረዳ ማእከል ጋር በጋራ እንደተዘጋጀ  በመግለጽ አርባምንጭ ማእከልን አመስግነዋል።

የማኅበረ ቅዱሳን አርባምንጭ ማእከል ጽ/ቤት ኃላፊ  ዲ/ን ችሮት አበራ በመልእክታቸው ማ/ቅ አርባምንጭ ማእከል በእግዚአብሔር ቸርነት ላለፉት 5 ወራት ከሚመለከታቸው የቤ/ን አካላት ጋር በመተባበር 8364 አዳዲሰ አማንያን ወደ ቅድስት ቤ/ክን እንዲቀላቀሉ አድርጓል በማለት በተጨማሪም ሌሎችም በርካታ መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎቶች መከናወናቸውን ጠቁመዋል።

አክለውም  በእንደዚህ አይነት ሐዋርያዊ አገልግሎት በዛሬው ዕለት የተመረቁ ሰባኪያነ ወንጌል በሚሰማሩበት አከባቢ በቋንቋቸው  በማስተማር  ለቅድስት ቤ/ክ ትልቅ ሚና እንዳላቸው ገልጸው ጠንክረው እንዲያገለግሉ መክረዋል።

BY ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)








Share with your friend now:
tgoop.com/mahibere_kidusan/8502

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Telegram has announced a number of measures aiming to tackle the spread of disinformation through its platform in Brazil. These features are part of an agreement between the platform and the country's authorities ahead of the elections in October. Telegram Android app: Open the chats list, click the menu icon and select “New Channel.” “[The defendant] could not shift his criminal liability,” Hui said. Activate up to 20 bots Among the requests, the Brazilian electoral Court wanted to know if they could obtain data on the origins of malicious content posted on the platform. According to the TSE, this would enable the authorities to track false content and identify the user responsible for publishing it in the first place.
from us


Telegram ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)
FROM American