MAHIBERE_KIDUSAN Telegram 8503
26 የደረጃ አንድ የሰባኪያነ ወንጌል ሠልጣኞች መመረቃቸውን በማኅበረ ቅዱሳን የአርባምንጭ ማእከል ገለጸ

የካቲት ፲፫/፳፻፲፯ ዓ.ም

በማኅበረ ቅዱሳን የአርባምንጭ ማእከል ከከምባ ወረዳ ማእከል ጋር በመተባበር በከምባና ጋርዳ ማርታ ወረዳዎች፣ ከተለያዩ አጥቢያዎችና የስብከት ወንጌል መስጫ ማእከላት ለተወጣጡ 26 የደረጃ አንድ የሰባኪያነ ወንጌል ሠልጣኞች የካቲት 12 ቀን /2017 ዓ.ም አስመርቋል ::

በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ የማኅበረ ቅዱሳን አርባምንጭ ማእከል ተወካይ፣ የከምባ ወረዳ ቤተክህነት ተወካይ እና የከምባ ወረዳ ማእከል ስራ አስፈጻሚዎች ተገኝተዋል።

በመርሐ ግብሩ በሠልጣኞች አጠር ያለ ትምህርተ ወንጌል የተሰጠ ሲሆን  ከአርባምንጭ ማእከል ስብከተ ወንጌል ዋና ክፍል በመ/ር መብራቱ “እኔ ከምሰጠው ውሃ የሚጠጣ ሁሉ ለዘለዓለም አይጠማም” በሚል ርዕስ ት/ተ ወንጌል ተሰጥጧል።

የከምባ ወረዳ ማዕከል ሰብሳቢ አቶ ቸርነት ጫሬ የወረዳ ማእከሉን መልዕክት አስተላልፈው ሥልጠናው የአርባምንጭ ማእከል ከከምባ ወረዳ ማእከል ጋር በጋራ እንደተዘጋጀ  በመግለጽ አርባምንጭ ማእከልን አመስግነዋል።

የማኅበረ ቅዱሳን አርባምንጭ ማእከል ጽ/ቤት ኃላፊ  ዲ/ን ችሮት አበራ በመልእክታቸው ማ/ቅ አርባምንጭ ማእከል በእግዚአብሔር ቸርነት ላለፉት 5 ወራት ከሚመለከታቸው የቤ/ን አካላት ጋር በመተባበር 8364 አዳዲሰ አማንያን ወደ ቅድስት ቤ/ክን እንዲቀላቀሉ አድርጓል በማለት በተጨማሪም ሌሎችም በርካታ መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎቶች መከናወናቸውን ጠቁመዋል።

አክለውም  በእንደዚህ አይነት ሐዋርያዊ አገልግሎት በዛሬው ዕለት የተመረቁ ሰባኪያነ ወንጌል በሚሰማሩበት አከባቢ በቋንቋቸው  በማስተማር  ለቅድስት ቤ/ክ ትልቅ ሚና እንዳላቸው ገልጸው ጠንክረው እንዲያገለግሉ መክረዋል።



tgoop.com/mahibere_kidusan/8503
Create:
Last Update:

26 የደረጃ አንድ የሰባኪያነ ወንጌል ሠልጣኞች መመረቃቸውን በማኅበረ ቅዱሳን የአርባምንጭ ማእከል ገለጸ

የካቲት ፲፫/፳፻፲፯ ዓ.ም

በማኅበረ ቅዱሳን የአርባምንጭ ማእከል ከከምባ ወረዳ ማእከል ጋር በመተባበር በከምባና ጋርዳ ማርታ ወረዳዎች፣ ከተለያዩ አጥቢያዎችና የስብከት ወንጌል መስጫ ማእከላት ለተወጣጡ 26 የደረጃ አንድ የሰባኪያነ ወንጌል ሠልጣኞች የካቲት 12 ቀን /2017 ዓ.ም አስመርቋል ::

በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ የማኅበረ ቅዱሳን አርባምንጭ ማእከል ተወካይ፣ የከምባ ወረዳ ቤተክህነት ተወካይ እና የከምባ ወረዳ ማእከል ስራ አስፈጻሚዎች ተገኝተዋል።

በመርሐ ግብሩ በሠልጣኞች አጠር ያለ ትምህርተ ወንጌል የተሰጠ ሲሆን  ከአርባምንጭ ማእከል ስብከተ ወንጌል ዋና ክፍል በመ/ር መብራቱ “እኔ ከምሰጠው ውሃ የሚጠጣ ሁሉ ለዘለዓለም አይጠማም” በሚል ርዕስ ት/ተ ወንጌል ተሰጥጧል።

የከምባ ወረዳ ማዕከል ሰብሳቢ አቶ ቸርነት ጫሬ የወረዳ ማእከሉን መልዕክት አስተላልፈው ሥልጠናው የአርባምንጭ ማእከል ከከምባ ወረዳ ማእከል ጋር በጋራ እንደተዘጋጀ  በመግለጽ አርባምንጭ ማእከልን አመስግነዋል።

የማኅበረ ቅዱሳን አርባምንጭ ማእከል ጽ/ቤት ኃላፊ  ዲ/ን ችሮት አበራ በመልእክታቸው ማ/ቅ አርባምንጭ ማእከል በእግዚአብሔር ቸርነት ላለፉት 5 ወራት ከሚመለከታቸው የቤ/ን አካላት ጋር በመተባበር 8364 አዳዲሰ አማንያን ወደ ቅድስት ቤ/ክን እንዲቀላቀሉ አድርጓል በማለት በተጨማሪም ሌሎችም በርካታ መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎቶች መከናወናቸውን ጠቁመዋል።

አክለውም  በእንደዚህ አይነት ሐዋርያዊ አገልግሎት በዛሬው ዕለት የተመረቁ ሰባኪያነ ወንጌል በሚሰማሩበት አከባቢ በቋንቋቸው  በማስተማር  ለቅድስት ቤ/ክ ትልቅ ሚና እንዳላቸው ገልጸው ጠንክረው እንዲያገለግሉ መክረዋል።

BY ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)








Share with your friend now:
tgoop.com/mahibere_kidusan/8503

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

For crypto enthusiasts, there was the “gm” app, a self-described “meme app” which only allowed users to greet each other with “gm,” or “good morning,” a common acronym thrown around on Crypto Twitter and Discord. But the gm app was shut down back in September after a hacker reportedly gained access to user data. During a meeting with the president of the Supreme Electoral Court (TSE) on June 6, Telegram's Vice President Ilya Perekopsky announced the initiatives. According to the executive, Brazil is the first country in the world where Telegram is introducing the features, which could be expanded to other countries facing threats to democracy through the dissemination of false content. Just as the Bitcoin turmoil continues, crypto traders have taken to Telegram to voice their feelings. Crypto investors can reduce their anxiety about losses by joining the “Bear Market Screaming Therapy Group” on Telegram. Add the logo from your device. Adjust the visible area of your image. Congratulations! Now your Telegram channel has a face Click “Save”.! Add up to 50 administrators
from us


Telegram ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)
FROM American