MESERETMEDIA Telegram 811
በኢቢሲ ውስጥ ያለውን የአንዳንድ ሰራተኞች የፎርጅድ ዶክመንት ያጋለጠው ሰራተኛ የሽብር ክስ ቀረበበት

(መሠረት ሚድያ)- የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) አንዳንድ ሰራተኞች ፎርጅድ ወይም እውቅና የሌለው የትምህርት ማስረጃ እንዳላቸው ያጋለጠው የተቋሙ ሰራተኛ ሌላ የሽብር ክስ ቀርቦበት ለእስር ተዳርጎ እንደነበር ታወቀ።

አቶ ወገን አበበ የተባለው የቀድሞው የተቋሙ ሰራተኛ ክሱ ቀርቦበት 52 ቀን ታስሮ ጥር 26/2017 ዓ/ም መለቀቁን ለመሠረት ሚድያ ተናግሯል።

"የተያዝኩት ተወልጄ ባደግኩባት ዲላ ከተማ ነው፣ ከላይ በመጣ ትእዛዝ ተብሎ ቤቴ ተበረበረ። ዲላ 5 ቀን ከታሰርኩ በኋላ ወደ ወላይታ ሶደ ተወሰድኩ፣ 3 ቀን ታስሬ ወደ ሀዋሳ የፌደራል ምርመራ ተወሰድኩ፣ ከዛም አንድ ሳምንት ሀዋሳ ታስሬ ወደ አዲስ አበባ ፌደራል ምርመራ ሜክሲኮ ተወሰድኩ" በማለት ያለፈበትን የእስር ሂደት አስረድቷል።

መሠረት ሚድያ የተመለከተው የክስ ወረቀት እንደሚለው አቶ ወገን በአማራ ክልል ከሚንቀሳቀሱ ፀረ ሰላም ቡድን አባሎች ጋር በመቀናጀት እና ቡድኑን በመምራት መጠርመሩን ይገልፃል።

ክሱ አክሎም "በሀገራችን የተለያዩ አካባቢዎች ጥቃት ለማድረስ ተልእኮ በመቀበል እና ቡድኑን በገንዘብ በማገዝ" እንዲሁም "በመላው ሀገራችን ሰላም እንደሌለ በማስመሰል ህዝብ በመንግስት ላይ እንዲነሳሳና ለሽብር ተግባራት የሚቀሰቅሱ የሀሰት ቪድዮ እና የድምፅ መልዕክት በማዘጋጀት እና በማህበራዊ ሚድያ በማሰራጨት" የሚሉ ውንጀላዎችን አካቷል።

ይሁንና አቶ ወገን ከ52 ቀን እስር በኋላ በ40 ሺህ ብር ዋስ ተለቀዋል።

"እኔ አማራ ክልል ሄጄ እንኳን አላውቅም፣ ዘመድም የለኝም" የሚለው አቶ ወገን እንኳን ለተለያዩ ቡድኖች የገንዘብ ድጋፍ ሊያደርግ ኢቢሲ ከስራው ካባረረው በኋላ ስራ እንኩዋን እንደሌለው ገልጿል።

ግለሰቡ ከወራት በፊት የአንዳንድ የኢቢሲ ሰራተኞች የፎርጂድ ዶክመንትን በተመለከተ ካጋለጠ በኋላ ተቋሙ መረጃውን ያወጣብኝ የቀድሞ ሰራተኞዬ "ተአማኒነቴ እንዲቀንስ አድርጓል" በማለት 10 ሚልዮን ብር ካሳ ይክፈለኝ ብሎ ክስ መስርቶ ነበር።

ይሁንና ራሱ ኢቢሲ ከወራት በፊት በተቋሙ ሰራተኞች ላይ ባደረገው የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጥ ሂደት የ400 ሰራተኞቹ ሰነድ ፎርጂድ/ሀሰተኛ መሆኑን እንዳረጋገጠ አንድ ሾልኮ የወጣ ዶክመንት ጠቁሞ ነበር።

ይህ ሆኖ እያለ የተቋሙ ሀላፊዎች እርምጃ እንዳይወሰድ ይህን መረጃው እንደደበቁ፣ በጥቆማ አቅራቢዎች ላይም ዛቻ እና ማስፈራርያ እያደረሱ እንደኮነ በወቅቱ የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ለጠቅላይ አቃቤ ህግ የፃፈው ደብዳቤ አሳውቆ ነበር።

መረጃን ከመሠረት!

Facts Matter!

@MeseretMedia



tgoop.com/meseretmedia/811
Create:
Last Update:

በኢቢሲ ውስጥ ያለውን የአንዳንድ ሰራተኞች የፎርጅድ ዶክመንት ያጋለጠው ሰራተኛ የሽብር ክስ ቀረበበት

(መሠረት ሚድያ)- የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) አንዳንድ ሰራተኞች ፎርጅድ ወይም እውቅና የሌለው የትምህርት ማስረጃ እንዳላቸው ያጋለጠው የተቋሙ ሰራተኛ ሌላ የሽብር ክስ ቀርቦበት ለእስር ተዳርጎ እንደነበር ታወቀ።

አቶ ወገን አበበ የተባለው የቀድሞው የተቋሙ ሰራተኛ ክሱ ቀርቦበት 52 ቀን ታስሮ ጥር 26/2017 ዓ/ም መለቀቁን ለመሠረት ሚድያ ተናግሯል።

"የተያዝኩት ተወልጄ ባደግኩባት ዲላ ከተማ ነው፣ ከላይ በመጣ ትእዛዝ ተብሎ ቤቴ ተበረበረ። ዲላ 5 ቀን ከታሰርኩ በኋላ ወደ ወላይታ ሶደ ተወሰድኩ፣ 3 ቀን ታስሬ ወደ ሀዋሳ የፌደራል ምርመራ ተወሰድኩ፣ ከዛም አንድ ሳምንት ሀዋሳ ታስሬ ወደ አዲስ አበባ ፌደራል ምርመራ ሜክሲኮ ተወሰድኩ" በማለት ያለፈበትን የእስር ሂደት አስረድቷል።

መሠረት ሚድያ የተመለከተው የክስ ወረቀት እንደሚለው አቶ ወገን በአማራ ክልል ከሚንቀሳቀሱ ፀረ ሰላም ቡድን አባሎች ጋር በመቀናጀት እና ቡድኑን በመምራት መጠርመሩን ይገልፃል።

ክሱ አክሎም "በሀገራችን የተለያዩ አካባቢዎች ጥቃት ለማድረስ ተልእኮ በመቀበል እና ቡድኑን በገንዘብ በማገዝ" እንዲሁም "በመላው ሀገራችን ሰላም እንደሌለ በማስመሰል ህዝብ በመንግስት ላይ እንዲነሳሳና ለሽብር ተግባራት የሚቀሰቅሱ የሀሰት ቪድዮ እና የድምፅ መልዕክት በማዘጋጀት እና በማህበራዊ ሚድያ በማሰራጨት" የሚሉ ውንጀላዎችን አካቷል።

ይሁንና አቶ ወገን ከ52 ቀን እስር በኋላ በ40 ሺህ ብር ዋስ ተለቀዋል።

"እኔ አማራ ክልል ሄጄ እንኳን አላውቅም፣ ዘመድም የለኝም" የሚለው አቶ ወገን እንኳን ለተለያዩ ቡድኖች የገንዘብ ድጋፍ ሊያደርግ ኢቢሲ ከስራው ካባረረው በኋላ ስራ እንኩዋን እንደሌለው ገልጿል።

ግለሰቡ ከወራት በፊት የአንዳንድ የኢቢሲ ሰራተኞች የፎርጂድ ዶክመንትን በተመለከተ ካጋለጠ በኋላ ተቋሙ መረጃውን ያወጣብኝ የቀድሞ ሰራተኞዬ "ተአማኒነቴ እንዲቀንስ አድርጓል" በማለት 10 ሚልዮን ብር ካሳ ይክፈለኝ ብሎ ክስ መስርቶ ነበር።

ይሁንና ራሱ ኢቢሲ ከወራት በፊት በተቋሙ ሰራተኞች ላይ ባደረገው የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጥ ሂደት የ400 ሰራተኞቹ ሰነድ ፎርጂድ/ሀሰተኛ መሆኑን እንዳረጋገጠ አንድ ሾልኮ የወጣ ዶክመንት ጠቁሞ ነበር።

ይህ ሆኖ እያለ የተቋሙ ሀላፊዎች እርምጃ እንዳይወሰድ ይህን መረጃው እንደደበቁ፣ በጥቆማ አቅራቢዎች ላይም ዛቻ እና ማስፈራርያ እያደረሱ እንደኮነ በወቅቱ የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ለጠቅላይ አቃቤ ህግ የፃፈው ደብዳቤ አሳውቆ ነበር።

መረጃን ከመሠረት!

Facts Matter!

@MeseretMedia

BY Meseret Media


Share with your friend now:
tgoop.com/meseretmedia/811

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Click “Save” ; How to Create a Private or Public Channel on Telegram? Telegram iOS app: In the “Chats” tab, click the new message icon in the right upper corner. Select “New Channel.” Co-founder of NFT renting protocol Rentable World emiliano.eth shared the group Tuesday morning on Twitter, calling out the "degenerate" community, or crypto obsessives that engage in high-risk trading. 2How to set up a Telegram channel? (A step-by-step tutorial)
from us


Telegram Meseret Media
FROM American