MESERETMEDIA Telegram 817
የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ መቃረቡን ተከትሎ አገልግሎት ላይ እንዳይውል በታገደ መርዝ በርካታ ሺህ ውሻዎች አዲስ አበባ ውስጥ እየተገደሉ መሆኑ ታወቀ

- መርዙ ወንዝ ዳር የሚበቅል ምግብ ሊበክል እንደሚችል ተሰግቷል

(መሠረት ሚድያ)- በአለም ጤና ድርጅት አገልግሎት ላይ እንዳይውል በታገደ መርዝ በርካታ ሺህ ውሻዎች አዲስ አበባ ውስጥ እየተገደሉ መሆኑን ከተለያዩ ቦታዎች የሚደርሱን ጥቆማዎች ያሳያሉ።

በኮሪደር ልማት ምክንያት እንደ ፒያሳ እና ካዛንችስ ያሉ ቦታዎች መፍረሳቸውን ተከትሎ መንገድ ላይ የቀሩ በርካታ ውሻዎች መኖራቸው ይታወቃል።

ይሁንና ቀጣዩን የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ለመሳተፍ የሚመጡ እንግዶች "ጎዳና ላይ እንዳያዩዋቸው" በሚል ከዚህ በፊት ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ በርካታ ሺህ ውሻዎች በመርዝ እየተገደሉ እንደሆነ ታውቋል።

ባለፈው ወር የፈረንሳዩ ፕሬዝደንት ኢማኑኤል ማክሮን ሊመጡ ሲልም ሲባልም በተመሳሳይ ብዙ ውሻዎችን በመርዝ መገደላቸው ታውቋል።

"መርዙ በአለም ጤና ድርጅት አገልግሎት ላይ እንዳይውል የታገደ ነው፣ እንዴትስ ወደ ሀገራችን ገባ የሚለው ጉዳይ አጠያያቂ ነው" ያሉት አንድ ጉዳዩን የሚከታተሉ ግለሰብ መርዙ ሰዎች እጅ ቢገባ በአንድ የሻይ ማንኪያ እሩብ በታች ሆነ መጠን ሺህ ህዝብ ሊጨርስ ይችላል ብለዋል።

"መርዙ ሽታ የሌለው በመሆኑ በምግብም ሆነ መጠጥ ውስጥ ሊገባና ሰዎችን ለመጉዳት ሊውል ይችላል። በዚህ መርዝ ያለ ሃጢያታቸው እየተገደሉ ያሉ ውሾች የሚጣሉበት ቦታ ሌላው አውሬ ምግብ ያገኘ መስሎት የሞተውን በድን ሲበላ እንደሚሞት፣ ተያይዞም አሞራዎች በልተውት የተረፋቸውን ወንዝ ላይ ቢጥሉት ውሃው የሚመረዝ መሆኑ ሊታወቅ ይሀገባል" በማለት ስጋታቸውን ገልፀዋል።

አክለውም ውሃው የከተማም ሆነ የገጠር የወንዝ ዳር አትክልት ልማት ላይ ሊውል ስለሚችል ተያያዥነቱ ረጅም በመሆኑ ህዝብ ሁሉ ይህንን ድርጊት እንዲኮንን ተማፅነዋል።

መረጃን ከመሠረት!

@MeseretMedia



tgoop.com/meseretmedia/817
Create:
Last Update:

የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ መቃረቡን ተከትሎ አገልግሎት ላይ እንዳይውል በታገደ መርዝ በርካታ ሺህ ውሻዎች አዲስ አበባ ውስጥ እየተገደሉ መሆኑ ታወቀ

- መርዙ ወንዝ ዳር የሚበቅል ምግብ ሊበክል እንደሚችል ተሰግቷል

(መሠረት ሚድያ)- በአለም ጤና ድርጅት አገልግሎት ላይ እንዳይውል በታገደ መርዝ በርካታ ሺህ ውሻዎች አዲስ አበባ ውስጥ እየተገደሉ መሆኑን ከተለያዩ ቦታዎች የሚደርሱን ጥቆማዎች ያሳያሉ።

በኮሪደር ልማት ምክንያት እንደ ፒያሳ እና ካዛንችስ ያሉ ቦታዎች መፍረሳቸውን ተከትሎ መንገድ ላይ የቀሩ በርካታ ውሻዎች መኖራቸው ይታወቃል።

ይሁንና ቀጣዩን የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ለመሳተፍ የሚመጡ እንግዶች "ጎዳና ላይ እንዳያዩዋቸው" በሚል ከዚህ በፊት ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ በርካታ ሺህ ውሻዎች በመርዝ እየተገደሉ እንደሆነ ታውቋል።

ባለፈው ወር የፈረንሳዩ ፕሬዝደንት ኢማኑኤል ማክሮን ሊመጡ ሲልም ሲባልም በተመሳሳይ ብዙ ውሻዎችን በመርዝ መገደላቸው ታውቋል።

"መርዙ በአለም ጤና ድርጅት አገልግሎት ላይ እንዳይውል የታገደ ነው፣ እንዴትስ ወደ ሀገራችን ገባ የሚለው ጉዳይ አጠያያቂ ነው" ያሉት አንድ ጉዳዩን የሚከታተሉ ግለሰብ መርዙ ሰዎች እጅ ቢገባ በአንድ የሻይ ማንኪያ እሩብ በታች ሆነ መጠን ሺህ ህዝብ ሊጨርስ ይችላል ብለዋል።

"መርዙ ሽታ የሌለው በመሆኑ በምግብም ሆነ መጠጥ ውስጥ ሊገባና ሰዎችን ለመጉዳት ሊውል ይችላል። በዚህ መርዝ ያለ ሃጢያታቸው እየተገደሉ ያሉ ውሾች የሚጣሉበት ቦታ ሌላው አውሬ ምግብ ያገኘ መስሎት የሞተውን በድን ሲበላ እንደሚሞት፣ ተያይዞም አሞራዎች በልተውት የተረፋቸውን ወንዝ ላይ ቢጥሉት ውሃው የሚመረዝ መሆኑ ሊታወቅ ይሀገባል" በማለት ስጋታቸውን ገልፀዋል።

አክለውም ውሃው የከተማም ሆነ የገጠር የወንዝ ዳር አትክልት ልማት ላይ ሊውል ስለሚችል ተያያዥነቱ ረጅም በመሆኑ ህዝብ ሁሉ ይህንን ድርጊት እንዲኮንን ተማፅነዋል።

መረጃን ከመሠረት!

@MeseretMedia

BY Meseret Media


Share with your friend now:
tgoop.com/meseretmedia/817

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

How to Create a Private or Public Channel on Telegram? bank east asia october 20 kowloon You can invite up to 200 people from your contacts to join your channel as the next step. Select the users you want to add and click “Invite.” You can skip this step altogether. With the “Bear Market Screaming Therapy Group,” we’ve now transcended language. On June 7, Perekopsky met with Brazilian President Jair Bolsonaro, an avid user of the platform. According to the firm's VP, the main subject of the meeting was "freedom of expression."
from us


Telegram Meseret Media
FROM American