MESERETMEDIA Telegram 821
በአየር መንገድ ግቢ ውስጥ ከአመራሮች እውቅና ውጪ ተነሳ የተባለው ፎቶ በእውቅና መደረጉን የሚያሳይ ደብዳቤ ወጣ

(መሠረት ሚድያ)- ከቀናት በፊት ሲያነጋግር የነበረው የአየር መንገድ ግቢ ውስጥ የተነሳው ፎቶ እንደተባለው "ከተቋሙ አመራሮች እውቅና ውጪ" ሳይሆን በእውቅና መደረጉን የሚያሳይ ደብዳቤ ለመሠረት ሚድያ ደርሷል።

የአየር መንገዱ የአዲስ አበባ ሽያጭ ክፍል ዳይሬክተር አቶ ግሩም አበበ ለሲቪል አቪዬሽን ደህንነት ዋና መምሪያ ዳይሬክተር ታህሳስ 25/2017 ዓ/ም በፃፉት ደብዳቤ አርቲስት ምህረት ታደሰ በአየር መንገድ የአየር ክልል ውስጥ የፎቶ ፕሮግራም እንድታደርግ መጠየቋን ያሳያል።

ደብዳቤው አክሎም የፎቶ ፕሮግራሙ ለአየር መንገዱ ማስታወቂያነት ስለሚጠቅም ታህሳስ  27/2017 ዓ/ም ቅጥር ግቢ ውስጥ ገብተው ፎቶ እንዲነሱ ይጠይቃል።

የፎቶ ፕሮግራሙ በዚህ ሁኔታ በተቋሙ እውቅና ቢካሄድም ተቋሙ ከትናንት በስቲያ በፌስቡክ ገፁ "የግለሰቧ የአየር መንገድ ግቢ ውስጥ የልደት ምስል ቀረጻ ከተቋሙ አመራሮች እውቅና ውጭ የተደረገ ነው" ማለቱ ግርታን ፈጥሯል።

በተጨማሪም የፎቶ ፕሮርግራሙ የግል የልደት ፕሮግራም መሆኑን አርቲስቷ በሶሻል ሚድያ ገጿ ላይ የገለፀች ቢሆንም ይህ በምን መልኩ ለአየር መንገዱ በማስታወቂያነት እንደሚጠቅም ግልፅ አልሆነም። 

ተቋሙ ለፎቶ ፕሮግራሙ ከአርቲስቷ ገንዘብ አለመቀበሉን እና ምንም አይነት ውል እንደሌለው በመግለጫው ላይ ገልፆ ነበር።

በርካታ የማህበራዊ ሚድያ ተጠቃሚዎች ድርጊቱን ከአየር የበረራ ክልል ደህንነት ጋር በማንሳት ጥያቄ ሲያቀርቡ ሌሎች ደግሞ በምን መስፈርት አንድ ግለሰብ የግል ልደት ከፍ ያለ ደህንነት በሚያስፈልገው አውሮፕላን ላይ ዲኮር በመስራት ተከበረ የሚል ጥያቄ አንስተዋል፣ በሌላ በኩል ደግሞ ክስተቱ ለአየር መንገዱ ጥሩ ማስታወቂያነት ውሏል ብለው ሀሳብ የሰጡም አልጠፉም።

መረጃን ከመሠረት!

@MeseretMedia



tgoop.com/meseretmedia/821
Create:
Last Update:

በአየር መንገድ ግቢ ውስጥ ከአመራሮች እውቅና ውጪ ተነሳ የተባለው ፎቶ በእውቅና መደረጉን የሚያሳይ ደብዳቤ ወጣ

(መሠረት ሚድያ)- ከቀናት በፊት ሲያነጋግር የነበረው የአየር መንገድ ግቢ ውስጥ የተነሳው ፎቶ እንደተባለው "ከተቋሙ አመራሮች እውቅና ውጪ" ሳይሆን በእውቅና መደረጉን የሚያሳይ ደብዳቤ ለመሠረት ሚድያ ደርሷል።

የአየር መንገዱ የአዲስ አበባ ሽያጭ ክፍል ዳይሬክተር አቶ ግሩም አበበ ለሲቪል አቪዬሽን ደህንነት ዋና መምሪያ ዳይሬክተር ታህሳስ 25/2017 ዓ/ም በፃፉት ደብዳቤ አርቲስት ምህረት ታደሰ በአየር መንገድ የአየር ክልል ውስጥ የፎቶ ፕሮግራም እንድታደርግ መጠየቋን ያሳያል።

ደብዳቤው አክሎም የፎቶ ፕሮግራሙ ለአየር መንገዱ ማስታወቂያነት ስለሚጠቅም ታህሳስ  27/2017 ዓ/ም ቅጥር ግቢ ውስጥ ገብተው ፎቶ እንዲነሱ ይጠይቃል።

የፎቶ ፕሮግራሙ በዚህ ሁኔታ በተቋሙ እውቅና ቢካሄድም ተቋሙ ከትናንት በስቲያ በፌስቡክ ገፁ "የግለሰቧ የአየር መንገድ ግቢ ውስጥ የልደት ምስል ቀረጻ ከተቋሙ አመራሮች እውቅና ውጭ የተደረገ ነው" ማለቱ ግርታን ፈጥሯል።

በተጨማሪም የፎቶ ፕሮርግራሙ የግል የልደት ፕሮግራም መሆኑን አርቲስቷ በሶሻል ሚድያ ገጿ ላይ የገለፀች ቢሆንም ይህ በምን መልኩ ለአየር መንገዱ በማስታወቂያነት እንደሚጠቅም ግልፅ አልሆነም። 

ተቋሙ ለፎቶ ፕሮግራሙ ከአርቲስቷ ገንዘብ አለመቀበሉን እና ምንም አይነት ውል እንደሌለው በመግለጫው ላይ ገልፆ ነበር።

በርካታ የማህበራዊ ሚድያ ተጠቃሚዎች ድርጊቱን ከአየር የበረራ ክልል ደህንነት ጋር በማንሳት ጥያቄ ሲያቀርቡ ሌሎች ደግሞ በምን መስፈርት አንድ ግለሰብ የግል ልደት ከፍ ያለ ደህንነት በሚያስፈልገው አውሮፕላን ላይ ዲኮር በመስራት ተከበረ የሚል ጥያቄ አንስተዋል፣ በሌላ በኩል ደግሞ ክስተቱ ለአየር መንገዱ ጥሩ ማስታወቂያነት ውሏል ብለው ሀሳብ የሰጡም አልጠፉም።

መረጃን ከመሠረት!

@MeseretMedia

BY Meseret Media


Share with your friend now:
tgoop.com/meseretmedia/821

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

To upload a logo, click the Menu icon and select “Manage Channel.” In a new window, hit the Camera icon. How to create a business channel on Telegram? (Tutorial) Matt Hussey, editorial director of NEAR Protocol (and former editor-in-chief of Decrypt) responded to the news of the Telegram group with “#meIRL.” Informative While the character limit is 255, try to fit into 200 characters. This way, users will be able to take in your text fast and efficiently. Reveal the essence of your channel and provide contact information. For example, you can add a bot name, link to your pricing plans, etc.
from us


Telegram Meseret Media
FROM American