tgoop.com/nahomrecords/5237
Last Update:
ዳዊት ጽጌን ጨምሮ የሙያ ባልደረቦቹ በአሜሪካ እውቅና ተሰጣቸው
#Ethiopia | ተወዳጁ ድምፃዊ ዳዊት ፅጌ የሙዚቃ አቀናባራው አበጋዝ ሺዎታ እና ፕሮሞተር ሰለሞን ገብረማሪያም (ኪንግ ሶሎን )ጨምሮ በሲያትል ከተማ እውቅና ተሰጣቸው ።
ደዊት ፅጌ በ2024 በአሜሪካን ከተሞች ያቀረባቸው የተሳኩ ዝግጅቶች በማስመልከት እና ልዩ ተስጦ ያለው ድምፃዊ በመሆኑ ለሙዚቃው ላበረከተው አስተዋፆ ጭምር እውቅና አግኝቷል።
የሙዚቃ አቅናባሪው አበጋዝ ሺዎታ በኢትዮጵያ የምርጥ ሙዚቃ አቀናባሪ በመሆኑ እና ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ላበረከተው ከፍተኛ አስተዋጽዖ እንዲሁ እውቅና በክብር ተሰጥቷቸዋል።
በተያያዘ ዜና - የኪንግ ሶሎ ፕሮሞሽን ባለቤት ፕሮሞተር ሰለሞን ላለፉት 10 ዓመት በሲያትል ውስጥ በርካታ ዝግጅቶችን በማዘጋጀት እውቅና ተሰጥቶታል። ( City of Seattle • Office of the Mayor) የሲያትል ከተማ የከንቲባ ጽ/ቤት ቢሮ እውቅናውን የሰጠ ሲሆን ምክትል ከቲባዋም (Adiam Emery ) በዝግጅቱ ላይ በመገኘት የእውቅና ሰርተፍኬቱን አበርክተው አድናቆታቸውን ለተሸላሚዎቹ ገልጸዋል።
ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ የሃያላኑዋ አሜሪካ ግዙፍ ኢኮኖሚ ከሚንቅሳቅስባቸው ዋንኛዋ ከተማ የሆነው ሲያትል ዋሽግተን ምክትል ከቲባዋ መሆናቸው ለኢትዮጵያን ትልቅ ኩራት መሆኑ ተግልጿል።
BY Nahom Records Inc
Share with your friend now:
tgoop.com/nahomrecords/5237