TIKVAHETHIOPIA Telegram 93962
" ቢያንስ 20 ኢትዮጵያውያን ሕይወታቸው አልፏል " - IOM

ከጅቡቲ የተነሳች ስደተኞችን የጫነች መርከብ የመን አቅራቢያ በደረሰባት የመስጠም አደጋ ቢያንስ 20 ኢትዮጵያውያን ሕይወታቸው ማለፉን ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (IOM) አሳወቀ።

ከአደጋው 15 ኢትዮጵያውያን እና ሁለት የመናውያን የጀልባዋ ቀዛፊ እና ረዳቱ መትረፋቸውም ተገልጿል።

35 ስደተኞችን አሳፍራ ከጅቡቲ የተነሳችው ጀልባ ዱባብ አቅራቢያ ባጋጠማት ብርቱ ነፋስ ለአደጋው መጋለጧን ተመላክቷል።

በየመናዊ ካፒቴን እና ረዳቱ አማካኝነት ከጅቡቲ የባሕር ጠረፍ ጀልባዋ ስደተኞች አሳፍራ ቅዳሜ ዕለት በምሽት ነበር ጉዞ የጀመረችው።

አደጋው በርካታ ስደተኞች የሚጋፈጡትን አሳዛኝ አደጋ እንደሚያሳይ የገለጸው ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (IOM) ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ለሕገወጥ ስደት መንስኤ ለሆኑ ችግሮች መፍትኄ እንዲፈልጉ ጥሪውን አቅርቧል።

በርካታ ኢትዮጵያውያን የተሻለ የኑሮ ሁኔታ ፍለጋ በጅቡቲ በኩል ወደ የተለያዩ የአረብ ሃገራት እንደሚሰደዱ በተደጋጋሚ ይነገራል።

ባለፈው ጥቅምት ወርም በተመሳሳይ አደጋ ከጅቡቲ የተነሱ 45 ኢትዮጵያውያን ስደተኞች የተሳፈሩበት ጀልባ በደረሰበት አደጋ ሕይወታቸው ማለፉ ይታወሳል። 

የየመን ባሕር አካባቢ ለስደተኞች አደገኛ ከሆኑ የባሕር መስመሮች አንዱ መሆኑን ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (IOM) አመልክቷል።

ኢትዮጵያውን ስደተኞች ላይ ስለደረሰው አደጋ ከኢትዮጵያ መንግሥት በኩል የተሰማ ነገር የለም።

መረጃው የዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ ነው።

@tikvahethiopia



tgoop.com/tikvahethiopia/93962
Create:
Last Update:

" ቢያንስ 20 ኢትዮጵያውያን ሕይወታቸው አልፏል " - IOM

ከጅቡቲ የተነሳች ስደተኞችን የጫነች መርከብ የመን አቅራቢያ በደረሰባት የመስጠም አደጋ ቢያንስ 20 ኢትዮጵያውያን ሕይወታቸው ማለፉን ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (IOM) አሳወቀ።

ከአደጋው 15 ኢትዮጵያውያን እና ሁለት የመናውያን የጀልባዋ ቀዛፊ እና ረዳቱ መትረፋቸውም ተገልጿል።

35 ስደተኞችን አሳፍራ ከጅቡቲ የተነሳችው ጀልባ ዱባብ አቅራቢያ ባጋጠማት ብርቱ ነፋስ ለአደጋው መጋለጧን ተመላክቷል።

በየመናዊ ካፒቴን እና ረዳቱ አማካኝነት ከጅቡቲ የባሕር ጠረፍ ጀልባዋ ስደተኞች አሳፍራ ቅዳሜ ዕለት በምሽት ነበር ጉዞ የጀመረችው።

አደጋው በርካታ ስደተኞች የሚጋፈጡትን አሳዛኝ አደጋ እንደሚያሳይ የገለጸው ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (IOM) ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ለሕገወጥ ስደት መንስኤ ለሆኑ ችግሮች መፍትኄ እንዲፈልጉ ጥሪውን አቅርቧል።

በርካታ ኢትዮጵያውያን የተሻለ የኑሮ ሁኔታ ፍለጋ በጅቡቲ በኩል ወደ የተለያዩ የአረብ ሃገራት እንደሚሰደዱ በተደጋጋሚ ይነገራል።

ባለፈው ጥቅምት ወርም በተመሳሳይ አደጋ ከጅቡቲ የተነሱ 45 ኢትዮጵያውያን ስደተኞች የተሳፈሩበት ጀልባ በደረሰበት አደጋ ሕይወታቸው ማለፉ ይታወሳል። 

የየመን ባሕር አካባቢ ለስደተኞች አደገኛ ከሆኑ የባሕር መስመሮች አንዱ መሆኑን ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (IOM) አመልክቷል።

ኢትዮጵያውን ስደተኞች ላይ ስለደረሰው አደጋ ከኢትዮጵያ መንግሥት በኩል የተሰማ ነገር የለም።

መረጃው የዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ ነው።

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA





Share with your friend now:
tgoop.com/tikvahethiopia/93962

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

With the “Bear Market Screaming Therapy Group,” we’ve now transcended language. How to create a business channel on Telegram? (Tutorial) So far, more than a dozen different members have contributed to the group, posting voice notes of themselves screaming, yelling, groaning, and wailing in various pitches and rhythms. Among the requests, the Brazilian electoral Court wanted to know if they could obtain data on the origins of malicious content posted on the platform. According to the TSE, this would enable the authorities to track false content and identify the user responsible for publishing it in the first place. Telegram Channels requirements & features
from us


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American