TIKVAHETHIOPIA Telegram 93974
TIKVAH-ETHIOPIA
የስራ ማቆም አድማ የመቱት ሰራተኞች ምን አሉ ? 🚨“ በቂ ደመወዝ አይደለም የምናገኘው። ከማክሮ ኢኮሮሚው ጋርም የሚመጣጠን ስላልሆነ ተመግበን ማደር አልቻልንም” - የሥራ ማቆም አድማ የመቱ ከ350 በላይ ሠራተኞች ➡️ “ በዚሁ ዙሪያ ስብሰባ ላይ ነኝ ” - ድርጅቱ በአይሰን ኤክስፕሪያንስ መሠረታዊ የሰራተኞች ማኀበር ሥር እንደሚተዳደሩ የገለጹ የሳፋሪኮም ኮልሴንተርና የሲምካርድ አፕሩቫል ከ350 በላይ…
#Update

🔴 “ በጥሩ ሁኔታ በመግባባት ጥያቄያቸው ተመልሷል ” - ማኀበሩ

🔵 “ 20% የደመወዝ ጭማሪ አድርገው በኋላ ደግሞ ሥራ ጀምረን ሌላውን ለማስተካከል ተስማምተናል ” - ሠራተኞቹ

“ ከየካቲት 1/2017 ዓ/ም ጀምሮ 20% የደመወዝ ጭማሪ የሚደረግ መሆኑን ስምምነት ላይ ደርሰናል ” - ፌደሬሽኑ

በአይሰን ኤክስፕሪያንስ መሠረታዊ መሠራተኞች ማኀበር ሥር የሚተዳደሩት የሳፋሪኮም ኮልሴንተርና የሲምካርድ አፕሩቫል ሠራተኞች በማኀበሩ ላይ ቅሬታ ማቅረባቸውን ከሰዓታት በፊት መረጃ አድርሰናችሁ ነበር። 

ቅሬታ የቀረበበት ማኀበሩ በወቅቱ ማብራሪያ ሳይሰጥ የቆዬ ሲሆን፣ በኋላ ለቀረበበት ቅሬታ በሰጠን ምላሽ፣ “ስምምነት ላይ ደርሰናል” ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

የማኀበሩ የሰው ኃብት አቶ በፍቃዱ አበራ፣ “ስብሰባ ላይ ነበርኩ። ውይይት ላይ የነበረ ጉዳይ ነው። ውይይቱም በሰላም ተጠናቋል” ብለዋል።

ሠራተኞቹ ብዙ ቅሬታ አላቸውና በምን ተስማማችሁ? ስንል ላቀረብንላቸው ጥያቄ በምላሻቸው፣ “አጠቃላይ እንደቀረፍን ነው ልነግርህ የምችለው። በጥሩ ሁኔታ በመግባባት ጥያቄያቸው ተመልሷል” ነው ያሉት።

ስምምነት ላይ ደርሳችኋል ስንል የጠየቅናቸው ሠራተኞቹ በበኩላቸው አሁንስ ምን አሉ ?

“ ተነጋግረናል ሥር ጀምረን ከዛ ለማስተካከል፡፡ 20% የደመወዝ ጭማሪ አደርገው በኋላ ደግሞ ሥራ ጀምረን ሌላውን ለማስተካከል ተስማምተናል፡፡

'የትራንስፖርት ጉዳይም ይስተካከላል፣ አሁን ባለው የሥራ ማቆም ምክንያት ማንም ሰው እንዳይባረር፣ ሌሎችንም ጥያቄዎች ደግሞ በኅብረት ስምምነት ገብተን እንፈታልን’ ብለው ሁሉም ሠራተኞች እንዲመለሱ ነው የስማማነው፡፡

ችግሩ ተፈትቷል፡፡ የሚዲያ ትኩረት አጣንና በመጨረሻ በማይሆን ነገርም መስማማት ግዴታ ሆነብን፡፡ ምክንያቱም ከዚህ በላይ ሥራ ካቆምንም የሥራ ዋስትና አይኖርም ብለን እጅ ሰጥተናል፡፡ 

አንገብጋቢው ጉዳይ የደመወዝ ጉዳይ ስለነበረ እሱ ላይ 20% ጭማሪ በቀጣይ ወር ኢፌክቲቭ እንደሚሆን፣ ከዚያ ውጪ ሌሎች የሚሻሻሉ ነገሮችን በውይይት ተቀራርበን መስራት አለብን በሚለው ተነጋግረናል ” ብለዋል።


የ20% ደመወዝ ጭማሪ እዳደረገላቸው ነው የገጹት ሠራተኞቹ፣ ይሄ እውነት ነው ? ስንል ላቀረብንላቸው ጥያቄ የማኀበሩ የሰው ኃብት፣ “ በዚህ ጉዳይ ምላሽ ከመስጠት እቆጠባለሁ ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በበኩሉ፣ ተደርጓል የተባለው የደመወዝ ጭማሪ ትክክል ነው? ሲል በውይይቱ ሲሳተፍ ለነበረው ለትራንስፓርትና መገናኛ ሠራተኛ ማኀበራት ኢንዱስትሪ ፌደሬሽን ጥያቄ አቅርቧል።

የፌደሬሽኑ ፕሬዜዳንት አቶ አባትሁን ታከለ ምን ምላሽ ሰጡ ?

“ ደመወዝ ጭማሪ በኀብረት ስምምነቱ የሚቀመጥ ነው። ኀብረት ሰምምነት አልነበረም። ወደፊት በኅብረት ስምምነት እንደምናስቀምጥ፣ ዘላቂ መፍትሄ እንደምናመጣ ተግባብተናል ከአሰሪው ጋ።

ነገር ግን ለጊዜው አሁን ያለውን ሁኔታ አገናዝበን አሰሪው ከታች ከ5% ተነስቶ ወደላይ ከፍ ብሎ፣ ሠራተኞም ከላይ ወደታች መጥተው፣ በኛም መሠረት ከየተካቲት 1/2017 ዓ/ም 20% የደመወዝ ጭማሪ የሚደረግ መሆኑን ስምነት ላይ ደርሰናል።

አሁን ሠራተኞቹ ወደ ሥራ እንዲመለሱ ስምምነት ላይ ተደርሷል። ከነገ ጀምሮ ሥራ ይገባሉ ”
ብለዋል።

ሠራተኞቹ ቅር የተሰኙባቸው ከደመወዝ ውጪ ያሉ ሌሎች ጉዳዮችን በተመለከተ በምን ተስማማችሁ! ስንል ላቀረብንላቸው ጥያቄ ፕሬዜዳንቱ ምላሽ ሰጥተዋል።

“ ሌሎች የተነሱ ወደ ዘጠኝ ጥያቄዎች ነበሩ፣ ለጊዜው በኅብረት ስምምነት ወደፊት የሚፈተለ አሉ። የትራንስፓርት ጉዳይም በኀብረት ስምምነት የሚፈታ ነው ” ብለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia



tgoop.com/tikvahethiopia/93974
Create:
Last Update:

#Update

🔴 “ በጥሩ ሁኔታ በመግባባት ጥያቄያቸው ተመልሷል ” - ማኀበሩ

🔵 “ 20% የደመወዝ ጭማሪ አድርገው በኋላ ደግሞ ሥራ ጀምረን ሌላውን ለማስተካከል ተስማምተናል ” - ሠራተኞቹ

“ ከየካቲት 1/2017 ዓ/ም ጀምሮ 20% የደመወዝ ጭማሪ የሚደረግ መሆኑን ስምምነት ላይ ደርሰናል ” - ፌደሬሽኑ

በአይሰን ኤክስፕሪያንስ መሠረታዊ መሠራተኞች ማኀበር ሥር የሚተዳደሩት የሳፋሪኮም ኮልሴንተርና የሲምካርድ አፕሩቫል ሠራተኞች በማኀበሩ ላይ ቅሬታ ማቅረባቸውን ከሰዓታት በፊት መረጃ አድርሰናችሁ ነበር። 

ቅሬታ የቀረበበት ማኀበሩ በወቅቱ ማብራሪያ ሳይሰጥ የቆዬ ሲሆን፣ በኋላ ለቀረበበት ቅሬታ በሰጠን ምላሽ፣ “ስምምነት ላይ ደርሰናል” ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

የማኀበሩ የሰው ኃብት አቶ በፍቃዱ አበራ፣ “ስብሰባ ላይ ነበርኩ። ውይይት ላይ የነበረ ጉዳይ ነው። ውይይቱም በሰላም ተጠናቋል” ብለዋል።

ሠራተኞቹ ብዙ ቅሬታ አላቸውና በምን ተስማማችሁ? ስንል ላቀረብንላቸው ጥያቄ በምላሻቸው፣ “አጠቃላይ እንደቀረፍን ነው ልነግርህ የምችለው። በጥሩ ሁኔታ በመግባባት ጥያቄያቸው ተመልሷል” ነው ያሉት።

ስምምነት ላይ ደርሳችኋል ስንል የጠየቅናቸው ሠራተኞቹ በበኩላቸው አሁንስ ምን አሉ ?

“ ተነጋግረናል ሥር ጀምረን ከዛ ለማስተካከል፡፡ 20% የደመወዝ ጭማሪ አደርገው በኋላ ደግሞ ሥራ ጀምረን ሌላውን ለማስተካከል ተስማምተናል፡፡

'የትራንስፖርት ጉዳይም ይስተካከላል፣ አሁን ባለው የሥራ ማቆም ምክንያት ማንም ሰው እንዳይባረር፣ ሌሎችንም ጥያቄዎች ደግሞ በኅብረት ስምምነት ገብተን እንፈታልን’ ብለው ሁሉም ሠራተኞች እንዲመለሱ ነው የስማማነው፡፡

ችግሩ ተፈትቷል፡፡ የሚዲያ ትኩረት አጣንና በመጨረሻ በማይሆን ነገርም መስማማት ግዴታ ሆነብን፡፡ ምክንያቱም ከዚህ በላይ ሥራ ካቆምንም የሥራ ዋስትና አይኖርም ብለን እጅ ሰጥተናል፡፡ 

አንገብጋቢው ጉዳይ የደመወዝ ጉዳይ ስለነበረ እሱ ላይ 20% ጭማሪ በቀጣይ ወር ኢፌክቲቭ እንደሚሆን፣ ከዚያ ውጪ ሌሎች የሚሻሻሉ ነገሮችን በውይይት ተቀራርበን መስራት አለብን በሚለው ተነጋግረናል ” ብለዋል።


የ20% ደመወዝ ጭማሪ እዳደረገላቸው ነው የገጹት ሠራተኞቹ፣ ይሄ እውነት ነው ? ስንል ላቀረብንላቸው ጥያቄ የማኀበሩ የሰው ኃብት፣ “ በዚህ ጉዳይ ምላሽ ከመስጠት እቆጠባለሁ ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በበኩሉ፣ ተደርጓል የተባለው የደመወዝ ጭማሪ ትክክል ነው? ሲል በውይይቱ ሲሳተፍ ለነበረው ለትራንስፓርትና መገናኛ ሠራተኛ ማኀበራት ኢንዱስትሪ ፌደሬሽን ጥያቄ አቅርቧል።

የፌደሬሽኑ ፕሬዜዳንት አቶ አባትሁን ታከለ ምን ምላሽ ሰጡ ?

“ ደመወዝ ጭማሪ በኀብረት ስምምነቱ የሚቀመጥ ነው። ኀብረት ሰምምነት አልነበረም። ወደፊት በኅብረት ስምምነት እንደምናስቀምጥ፣ ዘላቂ መፍትሄ እንደምናመጣ ተግባብተናል ከአሰሪው ጋ።

ነገር ግን ለጊዜው አሁን ያለውን ሁኔታ አገናዝበን አሰሪው ከታች ከ5% ተነስቶ ወደላይ ከፍ ብሎ፣ ሠራተኞም ከላይ ወደታች መጥተው፣ በኛም መሠረት ከየተካቲት 1/2017 ዓ/ም 20% የደመወዝ ጭማሪ የሚደረግ መሆኑን ስምነት ላይ ደርሰናል።

አሁን ሠራተኞቹ ወደ ሥራ እንዲመለሱ ስምምነት ላይ ተደርሷል። ከነገ ጀምሮ ሥራ ይገባሉ ”
ብለዋል።

ሠራተኞቹ ቅር የተሰኙባቸው ከደመወዝ ውጪ ያሉ ሌሎች ጉዳዮችን በተመለከተ በምን ተስማማችሁ! ስንል ላቀረብንላቸው ጥያቄ ፕሬዜዳንቱ ምላሽ ሰጥተዋል።

“ ሌሎች የተነሱ ወደ ዘጠኝ ጥያቄዎች ነበሩ፣ ለጊዜው በኅብረት ስምምነት ወደፊት የሚፈተለ አሉ። የትራንስፓርት ጉዳይም በኀብረት ስምምነት የሚፈታ ነው ” ብለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA






Share with your friend now:
tgoop.com/tikvahethiopia/93974

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

To edit your name or bio, click the Menu icon and select “Manage Channel.” How to Create a Private or Public Channel on Telegram? The optimal dimension of the avatar on Telegram is 512px by 512px, and it’s recommended to use PNG format to deliver an unpixelated avatar. Ng Man-ho, a 27-year-old computer technician, was convicted last month of seven counts of incitement charges after he made use of the 100,000-member Chinese-language channel that he runs and manages to post "seditious messages," which had been shut down since August 2020. Ng was convicted in April for conspiracy to incite a riot, public nuisance, arson, criminal damage, manufacturing of explosives, administering poison and wounding with intent to do grievous bodily harm between October 2019 and June 2020.
from us


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American