የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ሰባት አባላት ያሉት
የአጀንዳ አርቃቂ ኮሚቴን ሰየመ።
ግንቦት ፮ ቀን ፳፻ ፲ወ፯ ዓ.ም
ለ፳፻ ፲ወ፯ ዓ.ም የቅዱስ ሲኖዶስ ርክበ ካህንት ጉባኤ አጀንዳ በማርቀቅ እንዲያቀርቡ ሰባት ሊቃነ ጳጳሳትን የሰየመ ሲሆን ኮሚቴው በቋሚ ሲኖዶስ ተዘጋጅቶ የቀረበውን አጀንዳ በመመርመርና በማሻሻል ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በማቅረብ የሚያጸድቅ ይሆናል። የኮሚቴው አባላትም፦
፩.አቡነ ጎርጎርጎሬዎስ
፪.አቡነ ቀሌምንጦስ
፫.አቡነ ኤዎስጣቴዎስ
፬.አቡነ ኤልያስ(አርባምንጭ)
፭.አቡነ ሩፋኤል
፮.አቡነ ዜናማርቆስ
፯.አቡነ ኤልሳዕ ሲሆኑ ምልዓተ ጉባኤው ከአጀንዳዎቹ መጽደቅ በኋላ የቅዱስ ፓትርያርኩን የመግቢያ መልዕክትና የቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤትን ሪፖርት ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል።
የአጀንዳ አርቃቂ ኮሚቴን ሰየመ።
ግንቦት ፮ ቀን ፳፻ ፲ወ፯ ዓ.ም
ለ፳፻ ፲ወ፯ ዓ.ም የቅዱስ ሲኖዶስ ርክበ ካህንት ጉባኤ አጀንዳ በማርቀቅ እንዲያቀርቡ ሰባት ሊቃነ ጳጳሳትን የሰየመ ሲሆን ኮሚቴው በቋሚ ሲኖዶስ ተዘጋጅቶ የቀረበውን አጀንዳ በመመርመርና በማሻሻል ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በማቅረብ የሚያጸድቅ ይሆናል። የኮሚቴው አባላትም፦
፩.አቡነ ጎርጎርጎሬዎስ
፪.አቡነ ቀሌምንጦስ
፫.አቡነ ኤዎስጣቴዎስ
፬.አቡነ ኤልያስ(አርባምንጭ)
፭.አቡነ ሩፋኤል
፮.አቡነ ዜናማርቆስ
፯.አቡነ ኤልሳዕ ሲሆኑ ምልዓተ ጉባኤው ከአጀንዳዎቹ መጽደቅ በኋላ የቅዱስ ፓትርያርኩን የመግቢያ መልዕክትና የቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤትን ሪፖርት ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል።
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
ቋሚ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
“ናሁ ውስተ አድባር እገሪሆሙ ለሰብአ ዜና ወይዜንዉ ሰላመ እነሆ የምሥራችን የሚሰብክ ሰላምን የሚያወራ (ሚጠትን የሚናገር) ሰው እግሮች በተራሮች ላይ ናቸው"
(ትን.ናሆም 1፣15 ትርጓሜ ቅዱስ ዮሐንስ አወፈርቅ)
በውጭ አህጉረ ስብከት ተመድበው ሐዋርያዊ አገልግሎታቸውን በመፈጸም ላይ የሚገኙት ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ የኒውዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ 1 ብፁዕ አቡነ ቴዎፍሎስ (ዶ/ር) የሰሜን ካሊፎርኒያና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ የጆርጅያና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ ወደ ሀገር ቤት በመግባት ዓመታዊ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤን እንዲሳተፉ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በቅዱስ ሲኖዶስ በኩል ጥያቄ ማቅረቧ ይታወቃል፡፡
መንግሥትም ሀገራዊ ተቋማትን ለማጠናከር ያለው ቁርጠኝነት የጸና መሆኑን በገለጸበት መግለጫ እንደተመለከትነው የሀገራችንን ሰላም ለማጽናት፣ የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንን የታሪክ ገጽታ ለመጠበቅ ተቀራርቦ መነጋገር የተሻለ መፍትሔ መሆኑን ተረድቶ ሦስቱ ሊቃነ ጳጳሳት ወደ ሀገር ገብተው የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤን እንዲሳተፉ መፍቀዱን ተረድተናል፡፡
በመሆኑም መንግሥት ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ያቀረበችውን ጥያቄ ተቀብሎ ሦስቱ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ወደ ሀገር እንዲገቡ በመፍቀዱና ተግባራዊ ምላሽ በመስጠቱ ከፍ ያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡
ወደፊትም እግዚአብሔር በሰጠን ምድር፣ አባቶቻችን ባቆዩልን ሀገር አስተማማኝ ሰላም እንዲኖር ለሀገራችንና ለሕዝባችን በሚጠቅሙ ጉዳዮች ላይ ግንኙነታችንን በማጠናከር በጋራ : ለመሥራት ዝግጁዎች መሆናችንን እንገልጻለን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ግንቦት 7 ቀን 2017 ዓ.ም.
ቋሚ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
“ናሁ ውስተ አድባር እገሪሆሙ ለሰብአ ዜና ወይዜንዉ ሰላመ እነሆ የምሥራችን የሚሰብክ ሰላምን የሚያወራ (ሚጠትን የሚናገር) ሰው እግሮች በተራሮች ላይ ናቸው"
(ትን.ናሆም 1፣15 ትርጓሜ ቅዱስ ዮሐንስ አወፈርቅ)
በውጭ አህጉረ ስብከት ተመድበው ሐዋርያዊ አገልግሎታቸውን በመፈጸም ላይ የሚገኙት ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ የኒውዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ 1 ብፁዕ አቡነ ቴዎፍሎስ (ዶ/ር) የሰሜን ካሊፎርኒያና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ የጆርጅያና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ ወደ ሀገር ቤት በመግባት ዓመታዊ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤን እንዲሳተፉ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በቅዱስ ሲኖዶስ በኩል ጥያቄ ማቅረቧ ይታወቃል፡፡
መንግሥትም ሀገራዊ ተቋማትን ለማጠናከር ያለው ቁርጠኝነት የጸና መሆኑን በገለጸበት መግለጫ እንደተመለከትነው የሀገራችንን ሰላም ለማጽናት፣ የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንን የታሪክ ገጽታ ለመጠበቅ ተቀራርቦ መነጋገር የተሻለ መፍትሔ መሆኑን ተረድቶ ሦስቱ ሊቃነ ጳጳሳት ወደ ሀገር ገብተው የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤን እንዲሳተፉ መፍቀዱን ተረድተናል፡፡
በመሆኑም መንግሥት ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ያቀረበችውን ጥያቄ ተቀብሎ ሦስቱ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ወደ ሀገር እንዲገቡ በመፍቀዱና ተግባራዊ ምላሽ በመስጠቱ ከፍ ያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡
ወደፊትም እግዚአብሔር በሰጠን ምድር፣ አባቶቻችን ባቆዩልን ሀገር አስተማማኝ ሰላም እንዲኖር ለሀገራችንና ለሕዝባችን በሚጠቅሙ ጉዳዮች ላይ ግንኙነታችንን በማጠናከር በጋራ : ለመሥራት ዝግጁዎች መሆናችንን እንገልጻለን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ግንቦት 7 ቀን 2017 ዓ.ም.
በቤቱ የማያገባው ባለቤት የለም።
በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ኅብረት ሥር፦በሃይማኖት፣በጥምቀት፣በሜሮን፣በቁርባን፣በኅብረት፣በመስቀላዊት ሕይወት የምንኖር ሁላችንም የቤተ ክርስቲያን ልጆች ነን። ስለዚህ የቤተ ክርስቲያን ማንኛውም ጉዳይ ያገባናል። በኅብረታችን መካከል የሚደረገውን ነውርን መታገሥም ጽድቅ አይደለም። አድርባይነት እና አስመሳይነት ነው። ማስመሰል ደግሞ ምትሀታዊ ኑፋቄ ነው።
የቤተ ክርስቲያንን ጥፋት እያዩ መታገሥ ቸርነት አይደለም፤የእምነት መጉደል እና በመስቀላዊት ሕግ አለማመን ነው እንጂ። በቤቱ የማያገባው ባለቤት አለ ወይ? ካልደነዘዘ በስተቀር። የምእመናንን፣ የገዳማትን፣ የአብነት ደቀ መዛሙርትን.. ዕረፍት አልባ መከራ እያዩ ዝም ማለት ትህትና አይደለም። ይሄ በኦርቶዶክሳዊነት ኅብረት እና በዘለዓለም ተስፋ አለማመን ነው።
በአባትነት ስም ረቂቅ የአባትነት ሽፍታ የሆኑትን ዝም ማለት፦ ለአባቶች ክብር ሰጪነት አይደለም። የግድ የለሽነት ጥግ ነው እንጂ። ግድ የለሾች ደግሞ የፍዙዛን መናፍስት አምሳያዎች ናቸው።
ማንንም ሲያበላሽ እና ቤተ ክርስቲያንን ገደል ሲከታት እያዩ ይከፋዋል እያሉ ዝም ማለት የገዘፈ ስንፍናም ምንፍቅናም ነው። የቤተ መቅደሱ አደገኛ ቦዘኔዎችን ዝም ማለት ቸርነት አይደለም። በቤተ ክርስቲያን እናትነት አለማመን ነው።
ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ሄሮድስን መገሠጹ፣ቅዱስ ኤልያስ አክዓብን መገሠጹ፣መድኅን ክርስቶስ ቤተ መቅደሱ ገበያ ያደረጉትን "ቤቴ የጸሎት ቤት ይባላል እናንተ ግን የወንበዶች ዋሻ አደረጋችሁት። "ማቴ.፳፩፥፲፫ ብሎ ገልጾ በተአምራት ቤተ መቅደሱን ማንጻቱ ስህተት ነው? አይደለም። ነቢዩ ኤልያስም፣ መጥምቁ ዮሐንስም፣ መድኅን ጌታም ያሳዩን የጥብዓት እውነት መመሪያችን አይደለም ወይ?
በተለይም ጌታችን ካሳየን ሌላ ምሥክር ከየት ይመጣል? ከራስ በላይ ነፋስ እንደሆነ ከክርስቶስ በላይ አርአያ ከየት ይገኛል? በፍጹም። ከኤልያስ በላይ ነቢይ፣ከዮሐንስ መጥምቅ በላይስ ጥቡዕ ሐዋርያ ከየት ይመጣል?
"እንግዲህ በጎ መሥራትን አውቆ ለማይሠራው ሰው ኃጢአት ትሆንበታለች።"ያዕ.፬፥፲፯። ቤታችንን ከአጥፊዎች መጠበቅ ትክክለኛ ውሳኔ ነው። ሁሉም ክርስቲያን በያለበት ለዕቅበተ ቤተ ክርስቲያን አንድ መሆን አለበት። ስንጥር ሸንበቆ ለመመረኮዝ መሞከር ግን ድጋፍም አይሆንም ለእጅም አደገኛ ነው።
የኔታ ገብረ መድኅን እንየው
በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ኅብረት ሥር፦በሃይማኖት፣በጥምቀት፣በሜሮን፣በቁርባን፣በኅብረት፣በመስቀላዊት ሕይወት የምንኖር ሁላችንም የቤተ ክርስቲያን ልጆች ነን። ስለዚህ የቤተ ክርስቲያን ማንኛውም ጉዳይ ያገባናል። በኅብረታችን መካከል የሚደረገውን ነውርን መታገሥም ጽድቅ አይደለም። አድርባይነት እና አስመሳይነት ነው። ማስመሰል ደግሞ ምትሀታዊ ኑፋቄ ነው።
የቤተ ክርስቲያንን ጥፋት እያዩ መታገሥ ቸርነት አይደለም፤የእምነት መጉደል እና በመስቀላዊት ሕግ አለማመን ነው እንጂ። በቤቱ የማያገባው ባለቤት አለ ወይ? ካልደነዘዘ በስተቀር። የምእመናንን፣ የገዳማትን፣ የአብነት ደቀ መዛሙርትን.. ዕረፍት አልባ መከራ እያዩ ዝም ማለት ትህትና አይደለም። ይሄ በኦርቶዶክሳዊነት ኅብረት እና በዘለዓለም ተስፋ አለማመን ነው።
በአባትነት ስም ረቂቅ የአባትነት ሽፍታ የሆኑትን ዝም ማለት፦ ለአባቶች ክብር ሰጪነት አይደለም። የግድ የለሽነት ጥግ ነው እንጂ። ግድ የለሾች ደግሞ የፍዙዛን መናፍስት አምሳያዎች ናቸው።
ማንንም ሲያበላሽ እና ቤተ ክርስቲያንን ገደል ሲከታት እያዩ ይከፋዋል እያሉ ዝም ማለት የገዘፈ ስንፍናም ምንፍቅናም ነው። የቤተ መቅደሱ አደገኛ ቦዘኔዎችን ዝም ማለት ቸርነት አይደለም። በቤተ ክርስቲያን እናትነት አለማመን ነው።
ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ሄሮድስን መገሠጹ፣ቅዱስ ኤልያስ አክዓብን መገሠጹ፣መድኅን ክርስቶስ ቤተ መቅደሱ ገበያ ያደረጉትን "ቤቴ የጸሎት ቤት ይባላል እናንተ ግን የወንበዶች ዋሻ አደረጋችሁት። "ማቴ.፳፩፥፲፫ ብሎ ገልጾ በተአምራት ቤተ መቅደሱን ማንጻቱ ስህተት ነው? አይደለም። ነቢዩ ኤልያስም፣ መጥምቁ ዮሐንስም፣ መድኅን ጌታም ያሳዩን የጥብዓት እውነት መመሪያችን አይደለም ወይ?
በተለይም ጌታችን ካሳየን ሌላ ምሥክር ከየት ይመጣል? ከራስ በላይ ነፋስ እንደሆነ ከክርስቶስ በላይ አርአያ ከየት ይገኛል? በፍጹም። ከኤልያስ በላይ ነቢይ፣ከዮሐንስ መጥምቅ በላይስ ጥቡዕ ሐዋርያ ከየት ይመጣል?
"እንግዲህ በጎ መሥራትን አውቆ ለማይሠራው ሰው ኃጢአት ትሆንበታለች።"ያዕ.፬፥፲፯። ቤታችንን ከአጥፊዎች መጠበቅ ትክክለኛ ውሳኔ ነው። ሁሉም ክርስቲያን በያለበት ለዕቅበተ ቤተ ክርስቲያን አንድ መሆን አለበት። ስንጥር ሸንበቆ ለመመረኮዝ መሞከር ግን ድጋፍም አይሆንም ለእጅም አደገኛ ነው።
የኔታ ገብረ መድኅን እንየው
ማኀበረ ቅዱሳን ለሃይማኖታዊ ጥያቄ በስልክ ምላሽ የሚያገኙበት አገልግሎት አስጀመረ
#FastMereja I በማኅበረ ቅዱሳን የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ አገልግሎት የሚፈልጉትን ሃይማኖታዊ ጥያቄ በስልክ ቁጥር ደውለው ማብራሪያ የሚያገኙበት አገልግሎት ማስጀመሩን ፋስት መረጃ ሰምቷል።
«ሃሎ መምህር» የተሰኘው አገልግሎቱ እንዲመለስልዎ የሚፈልጉትን ሃይማኖታዊ ጥያቄ በስልክ ቁጥር 0111 55 32 32 በመደወል ለጥያቄዎ ማብራሪያ እና መልስ ከመምህራን ያገኛሉ ተብሏል።
ዘወትር ከሰኞ - አርብ ከጠዋቱ 4:00 እስከ ቀኑ 10:00 አገልግሎቱ የሚሰጥ ሲሆን ሰኞ፣ ረቡዕ እና ሐሙስ በአማርኛና በኦሮምኛ፣ ማክሰኞ እና ዓርብ በአማርኛ ቋንቋ ብቻ አግልግሎቱን ማግኘት ይችላሉ ተብሏል።
#FastMereja I በማኅበረ ቅዱሳን የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ አገልግሎት የሚፈልጉትን ሃይማኖታዊ ጥያቄ በስልክ ቁጥር ደውለው ማብራሪያ የሚያገኙበት አገልግሎት ማስጀመሩን ፋስት መረጃ ሰምቷል።
«ሃሎ መምህር» የተሰኘው አገልግሎቱ እንዲመለስልዎ የሚፈልጉትን ሃይማኖታዊ ጥያቄ በስልክ ቁጥር 0111 55 32 32 በመደወል ለጥያቄዎ ማብራሪያ እና መልስ ከመምህራን ያገኛሉ ተብሏል።
ዘወትር ከሰኞ - አርብ ከጠዋቱ 4:00 እስከ ቀኑ 10:00 አገልግሎቱ የሚሰጥ ሲሆን ሰኞ፣ ረቡዕ እና ሐሙስ በአማርኛና በኦሮምኛ፣ ማክሰኞ እና ዓርብ በአማርኛ ቋንቋ ብቻ አግልግሎቱን ማግኘት ይችላሉ ተብሏል።
የእስር ዜና!!!
ዲያቆን ታደሰ ወርቁ ታሰረ‼️
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በስብከት አገልግሎቱ፣በተለያዩ ስልጠናዎች ላይ ስልጠና በመስጠት፣በተለይም ተሃድሶውያንን በመዋጋት የምናውቀው ዲያቆን ታደሰ ወርቁ ዛሬ በፀጥታ ኃይሎች መወሰዱ ተሰማ።
እንደሚታወቀው የቅዱስ ሶኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በሚካሄድበት ወቅት በተለይም የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ በሚመረጥበት ግዜ ሁሉ ለቤተክርስቲያን ይታገላሉ የሚባሉ ወንድሞች እና እህቶች ይታሰራሉ። ዛሬም ዲያቆን ታደሰ ወርቁ ታስሯል።
የቅዱስ ሲኖዶስን ጸሐፊ እና የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅን መምረጥ የመንፈስ ቅዱስ እና የብፁዓን አባቶች ድርሻ ነው። በዚህ ወቅት የሚታሰር አንዳችም ሰው መኖር የለበትም ።ወንድማችንን እንድትፈቱት እንጠይቃለን ።
መንክር ሚዲያ-Menker Media
ዲያቆን ታደሰ ወርቁ ታሰረ‼️
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በስብከት አገልግሎቱ፣በተለያዩ ስልጠናዎች ላይ ስልጠና በመስጠት፣በተለይም ተሃድሶውያንን በመዋጋት የምናውቀው ዲያቆን ታደሰ ወርቁ ዛሬ በፀጥታ ኃይሎች መወሰዱ ተሰማ።
እንደሚታወቀው የቅዱስ ሶኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በሚካሄድበት ወቅት በተለይም የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ በሚመረጥበት ግዜ ሁሉ ለቤተክርስቲያን ይታገላሉ የሚባሉ ወንድሞች እና እህቶች ይታሰራሉ። ዛሬም ዲያቆን ታደሰ ወርቁ ታስሯል።
የቅዱስ ሲኖዶስን ጸሐፊ እና የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅን መምረጥ የመንፈስ ቅዱስ እና የብፁዓን አባቶች ድርሻ ነው። በዚህ ወቅት የሚታሰር አንዳችም ሰው መኖር የለበትም ።ወንድማችንን እንድትፈቱት እንጠይቃለን ።
መንክር ሚዲያ-Menker Media
በአንድ ቀን አርባ አራት ጥንዶች ጋብቻቸውን ይፈጽማሉ
#Ethiopia | የኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ ለሁለተኛ ጊዜ ያዘጋጀው የቅድመ ጋብቻ ትምህርቱን የወሰዱ አርባ አራት ጥንዶች የፊታችን ሐሙስ ግንቦት 21 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ በሚገኘው ቶታል ደብረ ገነት ቅድስት ሥላሴ ካቴደራል በቤተ ክርስቲያን ሥርዓት ጋብቻቸውን በስርዓተ ተክሊል እና በቅዱስ ቁርባን ይፈጽማሉ።
የኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ በትዳር ሕይወት ላይ ያተኮረ ጠቃሚ የቅድመ ጋብቻ ትምህርት በመስጠት ይታወቃል። ይህ ትምህርት ለተሳታፊዎቹ ዘላቂና የተሳካ ትዳር ለመመሥረት የሚያስፈልጉትን መሠረታዊ እውቀቶችና ክህሎቶች በመስጠት ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረክታል።
ይህ የብዙኃን ጋብቻ ከዚህ ቀደም ለመጀመሪያ ጊዜ ከሁለት አመት በፊት ጥር 28 ቀን 2015 ዓ.ም በደብረ ምጥማቅ ሰአሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያምና ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ካቴደራል ተካሂዷል።
#Ethiopia | የኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ ለሁለተኛ ጊዜ ያዘጋጀው የቅድመ ጋብቻ ትምህርቱን የወሰዱ አርባ አራት ጥንዶች የፊታችን ሐሙስ ግንቦት 21 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ በሚገኘው ቶታል ደብረ ገነት ቅድስት ሥላሴ ካቴደራል በቤተ ክርስቲያን ሥርዓት ጋብቻቸውን በስርዓተ ተክሊል እና በቅዱስ ቁርባን ይፈጽማሉ።
የኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ በትዳር ሕይወት ላይ ያተኮረ ጠቃሚ የቅድመ ጋብቻ ትምህርት በመስጠት ይታወቃል። ይህ ትምህርት ለተሳታፊዎቹ ዘላቂና የተሳካ ትዳር ለመመሥረት የሚያስፈልጉትን መሠረታዊ እውቀቶችና ክህሎቶች በመስጠት ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረክታል።
ይህ የብዙኃን ጋብቻ ከዚህ ቀደም ለመጀመሪያ ጊዜ ከሁለት አመት በፊት ጥር 28 ቀን 2015 ዓ.ም በደብረ ምጥማቅ ሰአሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያምና ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ካቴደራል ተካሂዷል።