tgoop.com/uthmanovich/3007
Last Update:
ሰይፍ በባይብል
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
47፥4 *"እነዚያንም የካዱትን በጦር ላይ ባገኛችሁ ጊዜ ጫንቃዎችን በኃይል ምቱ"*፡፡ فَإِذَا لَقِيتُمُ الَّذِينَ كَفَرُوا فَضَرْبَ الرِّقَابِ حَتَّىٰ
ሙሽሪኮች ምእመናንን በበድር ዘመቻ ላይ ሊዋጉ ሲመጡ አምላካችን አሏህ ለምእመናን፦ "እነዚያንም የካዱትን በጦር ላይ ባገኛችሁ ጊዜ ጫንቃዎችን በኃይል ምቱ" አላቸው፦
47፥4 *"እነዚያንም የካዱትን በጦር ላይ ባገኛችሁ ጊዜ ጫንቃዎችን በኃይል ምቱ"*፡፡ فَإِذَا لَقِيتُمُ الَّذِينَ كَفَرُوا فَضَرْبَ الرِّقَابِ حَتَّىٰ
በዚህ በድር ዘመቻ ላይ አሏህ መላእክትን ልኳል፥ ለምእመናን ሦስት ሺህ መላእክትን ለዘመቻው እንዲረዱ አድርጓል። ቢታገሱ እና ቢጠነቀቁ ደግሞ በአምስት ሺህ መላእክት እንደሚረዳ ተናግሯል፥ ሦስት ሺህ እና አምስት ሺህ ተከታታዮች ሲኾኑ እረድቷቸዋል፦
3፥123 በበድርም እናንተ ጥቂቶች ኾናችሁ ሳለ አላህ በእርግጥ ረዳችሁ፡፡ አላህንም ታመሰግኑ ዘንድ ፍሩት፡፡ وَلَقَدْ نَصَرَكُمُ اللَّهُ بِبَدْرٍ وَأَنتُمْ أَذِلَّةٌ ۖ فَاتَّقُوا اللَّهَ لَعَلَّكُمْ تَشْكُرُونَ
3፥124 ለምእምናን «ጌታችሁ በሦስት ሺህ መላእክት የተወረዱ ሲኾኑ ቢረዳችሁ አይበቃችሁምን?» በምትል ጊዜ አስታውስ፡፡ إِذْ تَقُولُ لِلْمُؤْمِنِينَ أَلَن يَكْفِيَكُمْ أَن يُمِدَّكُمْ رَبُّكُم بِثَلَاثَةِ آلَافٍ مِّنَ الْمَلَائِكَةِ مُنزَلِينَ
3፥125 «አዎን ብትታገሱ እና ብትጠነቀቁ ከዚህም ፍጥነታቸው ጠላቶቻችሁ ቢመጡባችሁ ጌታችሁ ምልክት ባላቸው አምስት ሺህ መላእክት ይረዳችኋል፡፡» بَلَىٰ ۚ إِن تَصْبِرُوا وَتَتَّقُوا وَيَأْتُوكُم مِّن فَوْرِهِمْ هَـٰذَا يُمْدِدْكُمْ رَبُّكُم بِخَمْسَةِ آلَافٍ مِّنَ الْمَلَائِكَةِ مُسَوِّمِينَ
8፥9 ከጌታችሁ ርዳታን በፈለጋችሁ ጊዜ «እኔ በሺህ መላእክት ተከታታዮች ሲኾኑ እረዳችኋለሁ» ሲል ለናንተ የተቀበላችሁን አስታውሱ፡፡ إِذْ تَسْتَغِيثُونَ رَبَّكُمْ فَاسْتَجَابَ لَكُمْ أَنِّي مُمِدُّكُم بِأَلْفٍ مِّنَ الْمَلَائِكَةِ مُرْدِفِينَ
እዚህ አንቀጽ ላይ "ሺህ" ተብሎ የተቀመጠው ቃል "አልፍ" أَلْف ሲሆን ሙጅመል ነው፥ በሙፈሰል ደግሞ "ሦስት" እና "አምስት" በሚለው የገባው ቃል "ኣላፍ" آلَاف ሲሆን መላእክቱ "ተከታታዮች" ሲሆኑ የሚለው በሦስት ሺህ እና በአምስት ሺህ ቁጥር መምጣታቸውን ያሳያል። በበድር ዘመቻ አምላካችን አሏህ ለእነዚህ መላእክት፦ "እኔ ከእናንተ ጋር ነኝና እነዚያን ያመኑትን አጽናኑ! በእነዚያ በካዱት ልቦች ውስጥ ፍርሃትን በእርግጥ እጥላለሁ፡፡ ከአንገቶችም በላይ ምቱ! ከእነርሱም የቅርንጫፎችን መለያልይ ሁሉ ምቱ" በማለት አዘዛቸው፦
8፥12 ጌታህ ወደ መላእክቱ «እኔ ከእናንተ ጋር ነኝና እነዚያን ያመኑትን አጽናኑ! በእነዚያ በካዱት ልቦች ውስጥ ፍርሃትን በእርግጥ እጥላለሁ፡፡ ከአንገቶችም በላይ ምቱ! ከእነርሱም የቅርንጫፎችን መለያልይ ሁሉ ምቱ!» ሲል ያወረደውን አስታውስ፡፡ إِذْ يُوحِي رَبُّكَ إِلَى الْمَلَائِكَةِ أَنِّي مَعَكُمْ فَثَبِّتُوا الَّذِينَ آمَنُوا ۚ سَأُلْقِي فِي قُلُوبِ الَّذِينَ كَفَرُوا الرُّعْبَ فَاضْرِبُوا فَوْقَ الْأَعْنَاقِ وَاضْرِبُوا مِنْهُمْ كُلَّ بَنَانٍ
ይህ በእንዲህ እንዳለ ሚሽነሪዎች ወቃሽና ነቃሽ ሆነው፦ "መላእክት እንዴት የሰው አንገት ይቀላሉ" በማለት ባዕዳና እንግዳ ያልሆነ እና ያረጀና ያፈጀ ጥያቄ ይጠይቃሉ፥ እኛም ስልመልስ ባይብል ስለ ሰይፍ የሚናገረውን ጠንቅቆ ካለማንበብ የሚመጣ ጥያቄ ነው በማለት እንመልሳለን። በባይብል የእግዚአብሔር መላእክት የተመዘዘ ሰይፍ በእጃቸው እንደሚይዙ ብዙ ቦታ ይናገራል፦
ዘኍልቍ 22፥23 አህያይቱም የእግዚአብሔርን መልአክ በመንገድ ላይ ቆሞ የተመዘዘም ሰይፍ በእጁ ይዞ አየች፤
ዘኍልቍ 22፥31 የእግዚአብሔርን መልአክ በመንገድ ላይ ቆሞ የተመዘዘም ሰይፍ በእጁ ይዞ አየ፤ ሰገደም፥ በግምባሩም ወደቀ።
ኢያሱ 5፥13 የተመዘዘ ሰይፍ በእጁ የያዘ ሰው በፊቱ ቆሞ ነበር"*።
1ኛ ዜና 21፥16 *"ዳዊትም ዓይኖቹን አነሣ፤ የእግዚአብሔር መልአክ በምድርና በሰማይ መካከል ቆሞ፥ የተመዘዘም ሰይፍ በእጁ ሆኖ ወደ ኢየሩሳሌም ተዘርግቶ አየ"*።
ይህ ሰይፍ አንባሻ ቆርሰው የሚያበሉበት ሳይሆን የሰው አንገት የሚቀሉበት ነው፥ በአንድ ወቅት የእግዚአብሔርም መልአክ ከአሦራውያንም ሰፈር መቶ ሰማንያ አምስት ሺህ ገደሎ ነበር፦
ኢሳይያስ 37፥36 *"የእግዚአብሔርም መልአክ ወጣ፥ ከአሦራውያንም ሰፈር መቶ ሰማንያ አምስት ሺህ ገደለ፤ ማለዳም በተነሡ ጊዜ፥ እነሆ፥ ሁሉ በድኖች ነበሩ"*።
ድርሳነ ዑራኤል ላይ መልአኩ ዑራኤል ሰይፍ ይዞ አንድ ሰውን፦ "ከሁለት ቦታ እቆርጥሃለው" ሲለው ይደመጣል፦
ድርሳነ ዑራኤል ዘሚያዚያ ገፅ 174 ቁጥር 11 *"ቅዱስ ዑራኤል በሚያስፈራ ግርማ የተሳለ ሰይፉን ይዞ፦ "አንተ የነገርኩህን ነገር ለምን አቦዘንከው? አሁንስ ከሁለት ቦታ እቆርጥሃለው" አለው"*።
BY 🎙uthmanovich የንፅፅር channal !!!🎓
Share with your friend now:
tgoop.com/uthmanovich/3007