YASIN_NURU Telegram 5210
" የነብያችን ﷺ ስም በክፉ ነገር ሲነሳ ነፍስያችንን መቆጣጠር ያቅተናል ፤ ሰብር ያሳጣናል። ሆኖም የምናደርገው ነገር ቢኖር ተንኳሾችን ለህግ እና ለህግ ማቅረብ ብቻ ነው " - ፌዴራል መጅሊስ

የፌዴራል መጅሊስ በእስልምና ሃይማኖት ላይ ትንኮሳ ፈጽሟል / በነብዩ ሙሀመድ ﷺ ላይ ክብረነክ ፀያፍ ንግግር አድርጓል ያለውን ግለሰብ ወደ ህግ ለማቅረብ እየሰራ መሆኑን ዛሬ በሰጠው መግለጫ አሳውቋል።

መጅሊስ ፤ " ህግና ህግን መሰረት ባደረገ መልኩ ክስ መስርተን እየሄድን ነው  " ያለ ሲሆን ምዕመኑ " በትዕግስት ዱአ በማድረግ እንዲጠብቅ ብሏል።

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዜዳንት ሸይኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ ምን አሉ ?

" ነብያችን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ከሁሉም በላይ ከማንም በላይ ከራሳችንም በላይ የምንወዳቸው እና የምናከብራቸው እስልምናችን እሳቸውን ካልወደድን እና ካልተቀበልን መኖር የማይችል ከነፍስያችን በላይ ህይወታችንን ለእሳቸው የምንሰጥ ነብያችን ስም በክፉ ነገር ሲነሳ ነፍስያችንን መቆጣጠር ያቅተናል ፤ ሰብር ያሳጣናል።

ሆኖም ግን የምናደርገው ነገር ቢኖር እንዲህ ያለ ተንኳሾችን የምናቀርበው ለህግ እና ለህግ ብቻ ነው። ህግ ባለበት ሀገር ለህግ ነው የምናቀርበው።

መጅሊሳችን ከዚህ በፊት ሲያደርግ እንደነበረው ሁሉ ዛሬም ሁለት ነገር ሰርቶ አሳልፏል። አንድ እንዲህ ያለ ትንኮሳ የማንቀበል መሆኑን እንደ ሙስሊም በሰፊ አውግዘናል ፤ ምንም ግለሰብ ቢሆንም። በሌላ በኩል መጅሊስ ህግና ህግን መሰረት ባደረገ መልኩ ክስ መስርቶ እየሄደበት ነው። መንግሥትም ቢሆን እየተናበብን እየሄድን እንደሆነ እያየን ነው።

ሀገር ለማበላሸት፣ አንድነትን ለማናጋት የሚተጋውን ትንሽ ቦታ ስለምትበቃ እስከዛሬ ተደብቆ ቢኖርም ነገ ከነገወዲያ መያዙ አይቀርም ኢንሻ አላህ ወተአላ። ስለዚህ እሱ ተይዞ በስርዓት ለፍርድ እስከሚቀርብ ድረስ ከኛ የሚጠበቀው በትዕግስት ዱአ እያደረግን መጠበቅ ነው።

በተለይ እኛ የሃይማኖት ተቋማት ደግሞ እንዲህ አይነት ትንኮሳ የሚፈጽሙት ሃይማኖትን ወክለው አይደለም፣ ተቋማትን ወክለው አይደለም፣ ተቋማት ልከዋቸው አይደለም፣ የተቋማትን ኃላፊነት ወስደው አይደለም የግል ትንኮሳ ነው። የግል ትንኮሳ ሰላም እንዲደፈርስ የማይሰራ ስራ ስለሌለ ይሄን ተከትለን እኛ አብሮነታችን፣ ትላንትና የነበረ የጋራ የአብሮ መተባበር ተጠናክሮ ይቀጥላል እንጂ እንደ ተንኳሾቹ ይሻክራል ብላችሁ የምታስቡ ከሆነ ተሳስታችኃል።

ማንም ይሁን ማንም የትኛውንም ሃይማኖት ወክሎ የተነገረ ስላልሆነ የግል ሚናው ስለሆነ በግሉ ባደረገው ዋጋ መጠን እርምጃ ይወሰድበታል እርምጃ ስንል ህጋዊ እርምጃ ማለት ነው " ብለዋል።

Tikvah

SHARE 🔗SHARE

JOIN: @yasin_nuru   
JOIN: @yasin_nuru 



tgoop.com/yasin_nuru/5210
Create:
Last Update:

" የነብያችን ﷺ ስም በክፉ ነገር ሲነሳ ነፍስያችንን መቆጣጠር ያቅተናል ፤ ሰብር ያሳጣናል። ሆኖም የምናደርገው ነገር ቢኖር ተንኳሾችን ለህግ እና ለህግ ማቅረብ ብቻ ነው " - ፌዴራል መጅሊስ

የፌዴራል መጅሊስ በእስልምና ሃይማኖት ላይ ትንኮሳ ፈጽሟል / በነብዩ ሙሀመድ ﷺ ላይ ክብረነክ ፀያፍ ንግግር አድርጓል ያለውን ግለሰብ ወደ ህግ ለማቅረብ እየሰራ መሆኑን ዛሬ በሰጠው መግለጫ አሳውቋል።

መጅሊስ ፤ " ህግና ህግን መሰረት ባደረገ መልኩ ክስ መስርተን እየሄድን ነው  " ያለ ሲሆን ምዕመኑ " በትዕግስት ዱአ በማድረግ እንዲጠብቅ ብሏል።

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዜዳንት ሸይኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ ምን አሉ ?

" ነብያችን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ከሁሉም በላይ ከማንም በላይ ከራሳችንም በላይ የምንወዳቸው እና የምናከብራቸው እስልምናችን እሳቸውን ካልወደድን እና ካልተቀበልን መኖር የማይችል ከነፍስያችን በላይ ህይወታችንን ለእሳቸው የምንሰጥ ነብያችን ስም በክፉ ነገር ሲነሳ ነፍስያችንን መቆጣጠር ያቅተናል ፤ ሰብር ያሳጣናል።

ሆኖም ግን የምናደርገው ነገር ቢኖር እንዲህ ያለ ተንኳሾችን የምናቀርበው ለህግ እና ለህግ ብቻ ነው። ህግ ባለበት ሀገር ለህግ ነው የምናቀርበው።

መጅሊሳችን ከዚህ በፊት ሲያደርግ እንደነበረው ሁሉ ዛሬም ሁለት ነገር ሰርቶ አሳልፏል። አንድ እንዲህ ያለ ትንኮሳ የማንቀበል መሆኑን እንደ ሙስሊም በሰፊ አውግዘናል ፤ ምንም ግለሰብ ቢሆንም። በሌላ በኩል መጅሊስ ህግና ህግን መሰረት ባደረገ መልኩ ክስ መስርቶ እየሄደበት ነው። መንግሥትም ቢሆን እየተናበብን እየሄድን እንደሆነ እያየን ነው።

ሀገር ለማበላሸት፣ አንድነትን ለማናጋት የሚተጋውን ትንሽ ቦታ ስለምትበቃ እስከዛሬ ተደብቆ ቢኖርም ነገ ከነገወዲያ መያዙ አይቀርም ኢንሻ አላህ ወተአላ። ስለዚህ እሱ ተይዞ በስርዓት ለፍርድ እስከሚቀርብ ድረስ ከኛ የሚጠበቀው በትዕግስት ዱአ እያደረግን መጠበቅ ነው።

በተለይ እኛ የሃይማኖት ተቋማት ደግሞ እንዲህ አይነት ትንኮሳ የሚፈጽሙት ሃይማኖትን ወክለው አይደለም፣ ተቋማትን ወክለው አይደለም፣ ተቋማት ልከዋቸው አይደለም፣ የተቋማትን ኃላፊነት ወስደው አይደለም የግል ትንኮሳ ነው። የግል ትንኮሳ ሰላም እንዲደፈርስ የማይሰራ ስራ ስለሌለ ይሄን ተከትለን እኛ አብሮነታችን፣ ትላንትና የነበረ የጋራ የአብሮ መተባበር ተጠናክሮ ይቀጥላል እንጂ እንደ ተንኳሾቹ ይሻክራል ብላችሁ የምታስቡ ከሆነ ተሳስታችኃል።

ማንም ይሁን ማንም የትኛውንም ሃይማኖት ወክሎ የተነገረ ስላልሆነ የግል ሚናው ስለሆነ በግሉ ባደረገው ዋጋ መጠን እርምጃ ይወሰድበታል እርምጃ ስንል ህጋዊ እርምጃ ማለት ነው " ብለዋል።

Tikvah

SHARE 🔗SHARE

JOIN: @yasin_nuru   
JOIN: @yasin_nuru 

BY ያሲን ኑሩ️️ YASIN NURU


Share with your friend now:
tgoop.com/yasin_nuru/5210

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Commenting about the court's concerns about the spread of false information related to the elections, Minister Fachin noted Brazil is "facing circumstances that could put Brazil's democracy at risk." During the meeting, the information technology secretary at the TSE, Julio Valente, put forward a list of requests the court believes will disinformation. Concise The imprisonment came as Telegram said it was "surprised" by claims that privacy commissioner Ada Chung Lai-ling is seeking to block the messaging app due to doxxing content targeting police and politicians. In 2018, Telegram’s audience reached 200 million people, with 500,000 new users joining the messenger every day. It was launched for iOS on 14 August 2013 and Android on 20 October 2013. Hui said the messages, which included urging the disruption of airport operations, were attempts to incite followers to make use of poisonous, corrosive or flammable substances to vandalize police vehicles, and also called on others to make weapons to harm police.
from us


Telegram ያሲን ኑሩ️️ YASIN NURU
FROM American